ጌታ ፡ ኢየሱሴ ፡ የናዝሬቱ ፡ መልካም (Gieta Eyesusie Yenazrietu Melkam)

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

አዝ፦ ጌታ ፡ ኢየሱሴ ፡ የናዝሬቱ ፡ መልካም
ልቤ ፡ ወደደህ ፡ አፈቀረህ ፡ በጣም
ከእጆችህ ፡ መዳፍ ፡ ምን ፡ ጊዜም ፡ አልወጣም

1. ነበልባል ፡ ዐይኖችህ ፡ ምንጊዜም ፡ ስራቸው
እኔን ፡ መንከባከብ ፡ እኔን ፡ መጠበቅ ፡ ነው
ጠላቴም ፡ አየና ፡ እንዳለኝ ፡ ረጂ
ሊያጠፋኝ ፡ አልቻለም ፡ በምኞት ፡ ቀረ ፡ እንጂ

አዝ፦ ጌታ ፡ ኢየሱሴ ፡ የናዝሬቱ ፡ መልካም
ልቤ ፡ ወደደህ ፡ አፈቀረህ ፡ በጣም
ከእጆችህ ፡ መዳፍ ፡ ምን ፡ ጊዜም ፡ አልወጣም

2. የእጆችህ ፡ መዳፍ ፡ አጥብቀው ፡ ይዘውኛል
ለጠላት ፡ መንጋጋ ፡ መቼ ፡ ይሰጡኛል
ይህን ፡ ሳይ ፡ ነው ፡ ጌታ ፡ ዛሬ፡ ከበፊቱ
ሬት ፡ የሆነብኝ ፡ ከአንተ ፡ መለየቱ

አዝ፦ ጌታ ፡ ኢየሱሴ ፡ የናዝሬቱ ፡ መልካም
ልቤ ፡ ወደደህ ፡ አፈቀረህ ፡ በጣም
ከእጆችህ ፡ መዳፍ ፡ ምን ፡ ጊዜም ፡ አልወጣም

3. በዓለም ፡ ፈተና ፡ ወይም ፡ በሥጋዬ
በጥፋት ፡ ውስጥ ፡ ሆኜ ፡ አልታዘዝ ፡ ብዬ
ጥፋተኛነቴን ፡ ባውቀው ፡ ባላውቀውም
ጉስቁል ፡ ብዬ ፡ ስታይ ፡ አልፈኸኝ ፡ አታውቅም

አዝ፦ ጌታ ፡ ኢየሱሴ ፡ የናዝሬቱ ፡ መልካም
ልቤ ፡ ወደደህ ፡ አፈቀረህ ፡ በጣም
ከእጆችህ ፡ መዳፍ ፡ ምን ፡ ጊዜም ፡ አልወጣም

4. ላንተው ፡ ባለኝ ፡ ፍቅር ፡ ሳደንቅ ፡ ጓጉቼ
እይልኝ ፡ ስጨነቅ ፡ ቃላቶቼን ፡ አጥቼ
ቃላቶች ፡ ቢያጥሩኝም ፡ ብቻ ፡ ተመስገን ፡ ነው
ኢየሱስን ፡ የሰጠኝ ፡ እግዚአብሔር ፡ ፍቅር ፡ ነው

አዝ፦ ጌታ ፡ ኢየሱሴ ፡ የናዝሬቱ ፡ መልካም
ልቤ ፡ ወደደህ ፡ አፈቀረህ ፡ በጣም
ከእጆችህ ፡ መዳፍ ፡ ምን ፡ ጊዜም ፡ አልወጣም