እግዚአብሔር ፡ ይሠራል (Egziabhier Yeseral)

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

አዝ፦ ገና ፡ እግዚአብሔር ፡ ይሠራል ፡ ገና ፡ ምኑን ፡ አየንና
እንግዳ ፡ ሥራውን ፡ ከቶ ፡ ያልታወቀውን
በሰዎች ፡ አዕምሮ ፡ ያልተገመተውን
እናያለን ፡ ገና ፡ ድንቅ ፡ ሥራውን ፡ ሲሰራ
ክብር ፡ ለእርሱ ፡ ይሁን

የተበተነውን ፡ ሕዝብ ፡ ይሰበስበዋል
በበረከት ፡ እጁ ፡ ከክፉ ፡ ያድነዋል
የተጠማች ፡ ነፍሱን ፡ እጅግ ፡ ያረካዋል
ለቅሶውን ፡ በደስታ ፡ ለውጦ ፡ ያጽናናዋል

አዝ፦ ገና ፡ እግዚአብሔር ፡ ይሠራል ፡ ገና ፡ ምኑን ፡ አየንና
እንግዳ ፡ ሥራውን ፡ ከቶ ፡ ያልታወቀውን
በሰዎች ፡ አዕምሮ ፡ ያልተገመተውን
እናያለን ፡ ገና ፡ ድንቅ ፡ ሥራውን ፡ ሲሰራ
ክብር ፡ ለእርሱ ፡ ይሁን

የበጐነት ፡ ዐይኑን ፡ በእኛ ፡ ላይ ፡ ያደርጋል
በሰጠንም ፡ ምድር ፡ በጽኑ ፡ ይተክለናል
እርሱንም ፡ የሚያውቅ ፡ ልብ ፡ ለእኛ ፡ ይሰጠናል
የከበረ ፡ ስሙን ፡ በእኛ ፡ ላይ ፡ ያጠራል

አዝ፦ ገና ፡ እግዚአብሔር ፡ ይሠራል ፡ ገና ፡ ምኑን ፡ አየንና
እንግዳ ፡ ሥራውን ፡ ከቶ ፡ ያልታወቀውን
በሰዎች ፡ አዕምሮ ፡ ያልተገመተውን
እናያለን ፡ ገና ፡ ድንቅ ፡ ሥራውን ፡ ሲሰራ
ክብር ፡ ለእርሱ ፡ ይሁን

ዳርቻችንንም ፡ ጌታችን ፡ አስፍቶ
ቁጥራችንን ፡ ደግሞ ፡ አብዝቶ ፡ አበርክቶ
ምሽጉን ፡ አፍርሶ ፡ ጠላትን ፡ አሳዶ
አይቀር ፡ ያሳየናል ፡ ወደ ፡ ጥልቁ ፡ አውርዶ

አዝ፦ ገና ፡ እግዚአብሔር ፡ ይሠራል ፡ ገና ፡ ምኑን ፡ አየንና
እንግዳ ፡ ሥራውን ፡ ከቶ ፡ ያልታወቀውን
በሰዎች ፡ አዕምሮ ፡ ያልተገመተውን
እናያለን ፡ ገና ፡ ድንቅ ፡ ሥራውን ፡ ሲሰራ
ክብር ፡ ለእርሱ ፡ ይሁን

ከለመንነውና ፡ ከአሰብነው ፡ ይልቅ
እጅግ ፡ አስበልጦ ፡ ለሚቻለው ፡ ማድረግ
ለእርሱ ፡ ከዘለዓለም ፡ እስከዘለዓለም
ክብርና ፡ ምሥጋና ፡ ይድረስ ፡ እንላለን

አዝ፦ ገና ፡ እግዚአብሔር ፡ ይሠራል ፡ ገና ፡ ምኑን ፡ አየንና
እንግዳ ፡ ሥራውን ፡ ከቶ ፡ ያልታወቀውን
በሰዎች ፡ አዕምሮ ፡ ያልተገመተውን
እናያለን ፡ ገና ፡ ድንቅ ፡ ሥራውን ፡ ሲሰራ
ክብር ፡ ለእርሱ ፡ ይሁን