በክብር ፡ ከፍ ፡ ብሎአልና (Bekeber Kef Beloalena)

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

አዝ፦ በክብር ፡ ከፍ ፡ ብሎአልና
እንዘምር ፡ ለእግዚአብሔር ፡ ምሥጋና (፪x)

ጠላት ፡ ሊያጠቃን ፡ በብርቱ ፡ ሲሮጥ
ኤርትራ ፡ ሞልቶ ፡ ልባችን ፡ ሲቀልጥ
የእኛማ ፡ ነገር ፡ አበቃ ፡ ስንል
ወርዶ ፡ ደረሰ ፡ አምላክ ፡ አዳነን

አዝ፦ በክብር ፡ ከፍ ፡ ብሎአልና
እንዘምር ፡ ለእግዚአብሔር ፡ ምሥጋና (፪x)

እጅግ ፡ ሲመኩ ፡ በፈረሳቸው
አላመለጡም ፡ ደረስንባቸው
ብለው ፡ በትዕቢት ፡ እየፎከሩ
ባሕር ፡ ዋጣቸው ፡ ሳይወጡ ፡ ቀሩ

አዝ፦ በክብር ፡ ከፍ ፡ ብሎአልና
እንዘምር ፡ ለእግዚአብሔር ፡ ምሥጋና (፪x)

ጠላታችንን ፡ ከባሕር ፡ ጥሎ
ያስጨነቀንን ፡ ሁሉ ፡ አስወግዶ
ዛሬ ፡ ዝማሬ ፡ ጉልበት ፡ ሆነልን
ያ ፡ ሁሉ ፡ አልፎ ፡ መዝሙር ፡ ዘመርን

አዝ፦ በክብር ፡ ከፍ ፡ ብሎአልና
እንዘምር ፡ ለእግዚአብሔር ፡ ምሥጋና (፪x)

ከዛ ፡ ባርነት ፡ ነጻ ፡ ያወጣን
ቀንበራችንን ፡ የሰበረልን
በድንቅ ፡ በተዓምር ፡ በድል ፡ የመራን
እግዚአብሔር ፡ ነው ፡ ለዚህ ፡ ያበቃን

አዝ፦ በክብር ፡ ከፍ ፡ ብሎአልና
እንዘምር ፡ ለእግዚአብሔር ፡ ምሥጋና (፪x)