Azeb Hailu/Embi/Temesgen
< Azeb Hailu | Embi
ጽድቅን እንዲያወራ ምላሴ: እንድትረካ እንድታርፍ ነፍሴ
የዋጀኸኝ አምላኬ መድህኔ: ከዚህች ዓለም አመጻ ኩነኔ
እንዳይረክስ በከንቱ ከንፈሬ: እንዳልጥለው ውድ እንቁውን ክብሬ
ዘመኔን በእጆችህ ያዝክና: አራመድከኝ በሕይወት ጐዳና
አዝ ተመስገን ተመስገን ተመስገን ልበልህ ደግሜ
ከኃጢአት በሽታ ተፈውሼ ባንተ ታክሜ (፪x)
እንድረዳ ማዳንህን እንዳውቀው: ልቦናዬን ወዳንተ የመለስከው
እንዳያልፈኝ የሕይወቴ መና: ህሊናዬን ለቃልህ አቀናህ
በረከሰው ዓለም የቀደስከኝ: በጽድቅ መንገድ ላይ የመራኸኝ
ከብዙዎች እኔ ተለይቼ: ዘምራለሁ መቅደስህ ገብቼ
አዝ ተመስገን ተመስገን ተመስገን ልበልህ ደግሜ
ከኃጢአት በሽታ ተፈውሼ ባንተ ታክሜ (፪x)
አልመኝም ከእንግዲህ ወደ ውጪ: ረክቻለሁ ጌታ አንተን መርጬ
የዓለምን ከንቱነት ኮተቷን: ንቄዋለሁ ከነማንነቷ
ወስኛለሁ ልኖር አስከብሬህ: ላፈራልህ ጣፋጭ መልካም ፍሬ
ደስ እንዲልህ ሁሌ በእኔ ጌታ: እገዛለሁ ፈቅጄ በደስታ
አዝ ተመስገን ተመስገን ተመስገን ልበልህ ደግሜ ከኃጢአት በሽታ ተፈውሼ ባንተ ታክሜ (፪x)