ለጌትነቱ (Legietenetu) - አዜብ ፡ ኃይሉ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አዜብ ፡ ኃይሉ
(Azeb Hailu)

Azeb Hailu 1.png


(1)

እምቢ
(Embi)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፭ (2002)
ቁጥር (Track):

(7)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአዜብ ፡ ኃይሉ ፡ አልበሞች
(Albums by Azeb Hailu)

አዝ፦ ለጌትነቱ ፡ ወሰን ፡ የለዉ
ይህንን ፡ አምላክ ፡ ማን ፡ ልበለዉ
በምንስ ፡ ቋንቋ ፡ ስለርሱ ፡ ላውራ
ታምራቶቹን ፡ የፍቅሩን ፡ ሥራ (፪x)

(አሃሃሃሃ) ፡ ከምድር ፡ ጫፍ ፡ እስከ ፡ ጫፍ
(አሃሃሃሃ) ፡ እርሱን ፡ ያመልካሉ
(አሃሃሃሃ) ፡ ትዕዛዙን ፡ ይሰማል
(አሃሃሃሃ) ፡ ንፋስ ፡ ማዕበሉ

የሰማይ ፡ ሠራዊት ፡ የሚያውጁለት
በጐነቱንና ፡ የርሱን ፡ ጌትነት (፪x)

አዝ፦ ለጌትነቱ ፡ ወሰን ፡ የለዉ
ይህንን ፡ አምላክ ፡ ማን ፡ ልበለዉ
በምንስ ፡ ቋንቋ ፡ ስለርሱ ፡ ላውራ
ታምራቶቹን ፡ የፍቅሩን ፡ ሥራ (፪x)

(አሃሃሃሃ) ፡ ክብርን ፡ እንዲያወሩ
(አሃሃሃሃ) ፡ ያበጃጀሃቸው
(አሃሃሃሃ) ፡ የሚያሞጋግሱህ
(አሃሃሃሃ) ፡ እንዴት ፡ ብዙ ፡ ናቸው

አእላፋት ፡ በሰማይ ፡ እልፎች ፡ በምድር
ድንቅ ፡ ነህ ፡ ይሉሃል ፡ አንተን ፡ እግዚአብሔር
አእላፋት ፡ በሰማይ ፡ እልፎች ፡ በምድር
ጌታ ፡ ነህ ፡ ይሉሃል ፡ አንተን ፡ እግዚአብሔር

አዝ፦ ለጌትነቱ ፡ ወሰን ፡ የለዉ
ይህንን ፡ አምላክ ፡ ማን ፡ ልበለዉ
በምንስ ፡ ቋንቋ ፡ ስለርሱ ፡ ላውራ
ታምራቶቹን ፡ የፍቅሩን ፡ ሥራ (፪x)

(አሃሃሃሃ) ፡ አፍ ፡ ያለው ፡ የሌለው
(አሃሃሃሃ) ፡ መልእክት ፡ አለኝ ፡ ይላል
(አሃሃሃሃ) ፡ የሰራኝ ፡ እግዚአብሔር
(አሃሃሃሃ) ፡ ነው ፡ ብሎ ፡ ያወራል

በግራና ፡ በቀኝ ፡ በሁሉም ፡ አቅጣጫ
ፍጥረት ፡ የሚያወራው ፡ ያንተን ፡ ችሎት ፡ ብቻ
በግራና ፡ በቀኝ ፡ በሁሉም ፡ አቅጣጫ
ፍጥረት ፡ የሚያወራው ፡ ያንተን ፡ ስልጣን ፡ ብቻ

አዝ፦ ለጌትነቱ ፡ ወሰን ፡ የለዉ
ይህንን ፡ አምላክ ፡ ማን ፡ ልበለዉ
በምንስ ፡ ቋንቋ ፡ ስለርሱ ፡ ላውራ
ታምራቶቹን ፡ የፍቅሩን ፡ ሥራ (፪x)